ግንቦት 8 2017
ከተገነቡ እስከ ሠላሣ ዓመታት ያስቆጠሩ አራት የመስኖ ፕሮጀክቶች የታሰበውን ያህል አገልግሎት እየሰጡ ባለመሆናቸው ኢትዮጵያ በአማካይ ከ48 ቢሊየን ብር በላይ በያመቱ እያጣች ነው ተባለ።
ከአራቱ ፕሮጀክቶች ሶስቱ አሁን ላይ ምንም አገልግሎት እየሰጡ እንዳልሆነ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ትላንት በካፒታል ሆቴል ይፋ ያደረገው ጥናት አሳይቷል።
የመስኖ ግድቦች በባህሪያቸው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚጠይቁ ስራዎች መሆናቸው ይጠቀሳል፡፡
በኢትዮጵያም በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ ግድቦች በተለያዩ አካባቢዎች አሉ።
እነዚህ የመስኖ ግድቦች የወጣባቸውን ገንዘብ ያህል አገልግሎት እየሰጡ ነው ወይ? የሚለው ግን ጥያቄ እንደሆነ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በካፒታል ሆቴል ይፋ ያደረገው ጥናት ይጠቁማል፡፡
Comments