ታህሳስ 24፣2017
አካል ጉዳተኞችን በተመለከተ ሊጠበቁላቸው ከሚገቡ መብቶቻቸው ውስጥ በሁሉም አገልግሎቶችና ስራዎች ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ ሊሰራበት ይገባል ተባለ፡፡
በተለይ አካል ጉዳተኞች በጥበብ ስራዎች ላይ የሚከውኗቸው ስራዎች የላቁ ቢሆኑም ተመልካች አገኝተው ወደ እውቅና ዘርፍ የሚመጡት ጥቂቶችን እንደሆኑ ተነግሯል፡፡
ዓለም አቀፉን የአካል ጉዳተኞች ቀን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንና ከዓለም ጋለሪ ጋር በመተባበር በተሰናዳ ኤግዚቢሽን የአካል ጉዳተኞችን መብቶች ማስከበር ላይ የተከወኑ ካሉ ስራዎች በአካል ጉዳተኞች የሚሰናዱ የጥበብ ስራዎችን መደገፍ አንዱ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
በኢግዚቢሽኑ ላይ በተለያየ የሙያ መስክ የተሰማሩና አካል ጉዳተኛ የሆኑ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን ስለ ጥበብ ስራዎቻቸውም ነግረውናል፡፡
በኤግዚቢሽኑ ላይ የቀረቡት የስዕል ስራዎች አካል ጉዳተኞች የሚገጥሟቸው የተለያዩ ፈተናዎች እንዲሁም ተስፋዎች ያንፀባረቁበት ነው፡፡
Comments