ታህሳስ 25፣2017
በአፋር ክልል ገቢረሱ ዞን የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ መከሰቱን ዞኑ ለሸገር ተናገረ፡፡
ዛሬ ማለዳ 3 ሰዓት አካባቢ በዞኑ ዱለሳ ወረዳ ሰጋንቶ ቀበሌ ላይ ነው እሳተ ገሞራው የፈነዳው ተብሏል፡፡
በተጠቀሰው አካባቢ ያሉ ተራራ ላይ አዳዲስ ፍንዳታዎች መኖራቸውን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዶ አሊ ነግረውናል፡፡
በፍንዳታው ከሚወጣ ጭስ ጋር አብሮ ጭቃ እየተትጎለጎለ ወደ ላይ ይፈናጠራል ያሉት አቶ አብዶ ጭቃው ሰውነት ላይ ካረፈ በጣም ያቃጥላል ይላሉ፡፡
ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ ዶፈን ተራራ ላይ የተለያዩ የእሳተ ጎመራ ፍንዳታዎች እንደተከሰቱ የተናገሩት የዞኑ አስተዳደሪ እሳቸው የሰሙት ግን ከማለዳው 3 ሰዓት ላይ የተከሰውን እንደሆነ ነግረውናል፡፡
Comments