ማሻሻያው ተቋሙ የሚገጥመውን የመድሃኒት ግዢ መስተጓጎል ያስቀርለታል ተብሏል
TRACK

ማሻሻያው ተቋሙ የሚገጥመውን የመድሃኒት ግዢ መስተጓጎል ያስቀርለታል ተብሏል

Avatar

ህዳር 18፣2017

የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሚያጋጥመውን የበጀት እጥረት ለማስተካል ተገልጋይ ተቋማት በዱቤ የሚወስዱትን መድሃኒት ገቢ በአግባቡ እንዲመልሱ እንዲሁም ባላቸው የበጀት አቅም ብቻ መድሃኒት እንዲያዙ የሚያስችል የማቋቋሚያ አዋጅ ማሻሻያ ተደረገለት፡፡

ማሻሻያው ተቋሙ የሚገጥመውን የመድሃኒት ግዢ መስተጓጎል ያስቀርለታል ተብሏል፡፡

ከመንግስት ምንም ዓይነት በጀት የማይመደበለትና በተገላባጭ ፈንድ መድኃኒቶችና የህክምና ግብዓቶችን ለመንግስት የጤና ተቋማት የሚያቀርበው የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሚያገኘውን የገቢ ምንጭ ለማሳደግ የአዋጅ ማሻሻያ ተደርጎለታል፡፡

በአብዛኛው የመንግስት የጤና ተቋማት መድሃኒቶችን በሚያቀርበው ተቋሙ ተቋማት የወሰዱትን እዳ በጊዜው ባለመመለሳቸው በአሰራሩ ላይ እንቅፋት ሲፈጥርበት እንደነበር በተደጋጋሚ ተናግሯል፡፡

ይህንን ችግር ይቀርፋል ሌሎችም ለአሰራሩ ያግዛሉ የተባለው ሃሳቦች የተካተቱበት የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትና የመድኃኒት ፈንድ ለማቋቋም የቀረበ አዋጅ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ፀድቋል፡፡

ረቂቅ አዋጁን ለምክር ቤቱ ያቀረቡት የጤና ማህበራዊ ልማት ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ ወርቅሰሙ ማሞ ናቸው፡፡

Comments

Avatar