ሚያዝያ 11፣2016
በፈጠራ ስራዎች የመብት ባለቤትነት ክፍያ ዙሪያ በተናጠል ሲሰሩ የቆዩ ሁለት ማህበራት በጋራ ለመንቀሳቀስ ተስማሙ።
ማህበራቱ የየራሳቸውን የፈጠራ መብት የክፍያ ቀመር አዘጋጅተው ሲንቀሰቃሱ መቆየታቸውንም ተጠቅሷል።
የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ማህበራቱን ለማግባባት ወራት የፈጀ የማግባባት ስራ ሰርቷል ተብሏል።
ማህበራቱ፤ የኢትዮጵያ የቅጂና ተዛማች መብቶች የጋራ አስተዳደር ማህበር እና የኢትዮጵያ የሙዚቃ፣ የቅጂና ተዛማጅ መብቶች የጋራ አስተዳደር ማህበር ናቸው፡፡
ህጋዊ ምዝገባ ያላቸው እና የጥበብ ባለሞያዎችን የሚወከሉት እነዚህ ማህበራት የስነ ፅሁፍ፣ የኪነ ጥበብ እና ተመሳሳይ የፈጠራ ስራዎች በመብት ባለቤቱ ስምምነት እና በክፍያ በቴሌቭዥን፣ በራዲዮ፣ በትራንስፖርት ድርጅቶች፣ በምሸት ክበቦች፣ በልዩ ልዩ መዝናኛ ቤቶች ወዘተ ለህዝብ አገልግሎት እንዲቀርቡ ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸው ተነግሯል።
ከማህበራቱ አንደኛው በተለይ በሙዚቃ ስራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን የሚናገሩት የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር፤ አቶ ወልዱ ይመስል ሌላኛው ደግሞ በሁሉም የጥበብ ውጤቶች ዙሪያ የሚሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
Comments