የንብረት ታክስ አዋጅ በህብረተሰቡ ለተደራረበ ግብር እንዲጋለጥ ምክንያት እንዳይሆን ስጋት መፍጠሩ ተነገረ
TRACK

የንብረት ታክስ አዋጅ በህብረተሰቡ ለተደራረበ ግብር እንዲጋለጥ ምክንያት እንዳይሆን ስጋት መፍጠሩ ተነገረ

Avatar

ታህሳስ 18፣2017

የንብረት ታክስ አዋጅ በህብረተሰቡ ለተደራረበ ግብር እንዲጋለጥ ምክንያት እንዳይሆን ስጋት መፍጠሩ ተነገረ፡፡

የተጋነነ ነው የተባለው የንብረት ታክስ ምጣኔ በታችኛው የህብረተሰብ ክፍል ላይ ጫናውን እንደሚያበረታው በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ተገኝተው በረቂቅ አዋጁ ላይ አስተያታቸውን የሰጡ ተሳታፊዎች ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም ከተማ አስተዳደሮች ያለባቸውን ወጪ መሰረት አድርገው በየዓመቱ የንብረት ግብር ላይ ተመን እንዲያወጡ መፈቀዱ ለመልካም አስተዳደር ችግር ያጋልጣል ተብሏል፡፡

ትዕግስት ዘሪሁን

Comments

Avatar