ሰኔ 12 2017
ያልፍልኛል ነገዬ የተሻለ ይሆናል ብለው በህጋዊም ሆነ በህገ ወጥ መንገድ ባህር ተሻግረው ወደ አረብ ሀገራት እና ሌሎችም ሀገራት የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ቀላል የሚባል አይደለም፡፡
በህገ-ወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጡት ኢትዮጵያውያን ቀን ሌት ሳይሉ ተጉዘው፣ ባህር አቋርጠው እድል ከቀናቸው ያሰቡበት ቦታ ይደርሳሉ፡፡
እዚያ ከደረሱ በኋላም ግን ሁሉም ነገር እንዳሰቡት ሳይሆንላቸው ይቀርና ብዙ ፈተናዎችን ይጋፈጣሉ፡፡
ገሚሱ ሰውነቱ ላይ ጣል ያደረገውን ጨርቅ ብቻ ይዞ ባዶ እጁን ወደ ሀገሩ ይመለሳል፣ ገሚሱ ህይወቱን ያጣል፣ ከፊሉ ደግሞ የጤና መታወክ ያጋጥማቸው እና ወደ ሀገራቸው ይመለሳሉ፡፡
በህጋዊ የሚሄዱትም ቢሆን እንደዚህ ዓይነት ችግሮች ሲያጋጥማቸው ማየት አልያም ደግሞ ረጅም ዓመታትን ሰርተው ምንም ዓይነት አንጡራ ሀብት ሳይኖራቸው ይመለሳሉ፡፡
Comments