TRACK
የተሽከርካሪዎች የጭነት ክብደት መጠን ለመወሰንና ለመቆጣጠር ተብሎ የወጣው ደንብ የኑሮ ውድነቱን ያባብሰዋለል በሚል የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ተቃውሞ አቀረቡ።
ህዳር 3፣ 2017
የተሽከርካሪዎች የጭነት ክብደት መጠን ለመወሰንና ለመቆጣጠር ተብሎ የወጣው ደንብ የኑሮ ውድነቱን ያባብሰዋለል በሚል የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ተቃውሞ አቀረቡ።
የተሽከርካሪዎችን የጭነት ክብደት መጠን ለመወሰን እና ለመቆጣጠር የወጣው ደንብ አንድ ተሽከርካሪ ከ350 ኩንታል ወይንም ከ35 ቶን በላይ መጫንን የሚከለክል ነው።
በዚህ ጉዳይ ላይ ያነጋገርናቸው የተሽከርካሪ ባለንብረቶችም የተሽከርካሪ የጭነት ክብደት መጠን ገደብ መጣሉ ለተሽከርካሪዎች እና ለመንገዶች ደህንነት ታስቦ ቢሆንም የጭነት መጠኑ ላይ የተወሰነ መሻሻል መደረግ አለበት ብለዋል።
ይህ ካልሆነ ግን የኑሮ ውድነቱን ያባብሰዋል ሲሉ ነግረውናል።
Comments