በአዲስ አበባ ዘላቂ ማረፊያ የቀብር ስፍራዎች መናፈሻ ሊሆኑ ነው ተባለ
TRACK

በአዲስ አበባ ዘላቂ ማረፊያ የቀብር ስፍራዎች መናፈሻ ሊሆኑ ነው ተባለ

Avatar

ህዳር 18፣2017

የቀብር ስፍራዎች መናፈሻ ሊሆኑ ነው ተባለ፡፡

በአዲስ አበባ ዘላቂ ማረፊያ የሆኑ የቀብር ስፍራዎች የሚያምር ገፅታ ኖሯቸው መናፈሻ እንዲሆኑ እየተሰራ ቢሆንም ‘’ሙታንን የሚያውኩ ነገሮች’’ በህግ ያስቀጣሉ ተብሏል፡፡

የቀጨኔ ዘላቂ ማረፊያ ውስጥ ገብተው በመጨፈር ማህበራዊ ትስስት ሚድያ ላይ የለቀቁ ግለሰቦችም በህግ ጥላ ስር መሆናቸውም ለዚህ ማሳያ ነው ተብሏል፡፡

ቀብር የሚፈፀምባቸው ስፍራዎች በአብዛኛው ሰወር ያሉ፣ በደንና ቁጥቋጦዎች የተሞሉ እንደመሆናቸው አስገድዶ መድፈርና ሌላውም ወንጀል ሲፈፀምባቸው እንደነበር ሲነገር ይደመጣል፡፡

እነዚህን ስፍራዎች ከነበራቸው አስፈሪ ገፅታ ወደ መናፈሻነት ለመቀየር እየተሰራ መሆኑን በአዲስ አበባ ካሉ የቀብር ስፍራዎች መካከል አንዱ የሆነው የቀጨኔ ዘላቂ ማረፊያ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ድሪባ ገመቹ ነግረውናል፡፡

‘’እውነት ነው የቀብር ስፍራዎቹ ለወንጀል ድርጊት የተመቹ ነበሩ፤ አሁን ግን ቦታውን ወደ መናፈሻነት ቀይረነዋል፣ ባሉን 17 የሚደርሱ የጥበቃ ባለሙያዎች ጥብቅ ቁጥጥር እያደረግን ነው’’ ብለዋል፡፡

ቦታው ሰዎች ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ በኋላ አስከሬናቸው በክብር እንዲያርፍ ታስቦ የተሰናዳ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ድሪባ ‘’ምንም አይነት ሙታንን የሚረብሹ ተግባራት’’ በህግ የሚያስጠይቁ መሆኑን በቅርቡ በመቃብር ስፍራው ሲጨፍሩ በመቅረፅ በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ ሰዎችን ጉዳይ በማንሳት አስረድተዋል፡፡

Comments

Avatar