ሰኔ 19፣ 2016
ከዓመት ዓመት የተለያዩ ማሻሻያዎች እየተደረጉለት ነው የሚባለው የኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅርቦት ዘርፍ አሁንም ፈተናዎች አላጡትም፡፡
በየጤና ተቋማቱ የሚፈለጉ መድኃኒቶች እንደልብ ማግኘት አስቸጋሪ ሆኖ ዘልቋል፡፡
ከዓለም አቀፍና ከሀገር ቤት አቅራቢዎች በጨረታ መድኃኒት የምትሸምተው ኢትዮጵያ በተጨማሪም የሀገር ቤት አምራቾችን በማበርታት በዘርፉ የሚታየውን የአቅርቦት ችግር ለመፍታት እንድትሰራ ተመክራለች፡፡
ለብዙ ዓመታት በመድኃኒት አቅርቦት ሥርዓቱ ውስጥ ከሚነሱ ችግሮች ውስጥ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ዋነኛው ሆኖ ቀጥሏል፡፡
ይህም ከውጭ የሚገዙትን ጨምሮ ለሀገር ቤት የመድኃኒት ምርቱም ዋነኛ ፈተና መሆኑ ተነግሯል፡፡
Comments