TRACK
ስምምነት ተደርሶ የነበረ ቢሆንም ስምምነቱ እንደተደረሰ በኢትዮጵያ እና በሱዳን ውስጥ የነበሩ ጦርነቶች ወደ ትግበራ እንዳይገባ ችግር ሆኗል ብለዋል
ሰኔ 25፣ 2016
በድንበር አካባቢ የሚነሱ የእንስሳት በሽታዎችን ለመከላከል ከሱዳን በስተቀር ከሁሉም ጎረቤት ሀገራት ጋር እየተሰራ ነው ተባለ፡፡
ይህንን ያለው የግብርና ሚኒስቴር ነው፡፡
ግብርና ሚንስቴር ድንበር አካባቢ የሚነሱ የእንስሳት በሽታዎችን ለመከላከል የሚያስችለውን ስምምነቱ ከሁሉም ጎረቤት ሀገራት ጋር ተፈራርሞ እየሰራ መሆኑን ሰምተናል፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ እንደነገሩን ከሱዳን ጋር ተመሳሳይ ስምምነት ተደርሶ የነበረ ቢሆንም ስምምነቱ እንደተደረሰ በኢትዮጵያ እና በሱዳን ውስጥ የነበሩ ጦርነቶች ወደ ትግበራ እንዳይገባ ችግር ሆኗል ብለዋል፡፡
Comments