ጥቅምት 26 2018
የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ከማህበረሰቡ ከሚቀርቡለት የተበደልን አቤቱታዎች 35 በመቶዎቹ እኔን የሚመለከቱ አይደሉም አለ፡፡
በህግ የተሰጠኝ ሃላፊነት የግልም ሆነ የመንግስት ድርጅቶች ማህበረሰቡ ላይ የሚፈፅሟቸውን አስተዳደራዊ በደሎች የተመለከቱ አቤቱታዎችን ተቀብሎ በመመርመር የተበዳዮችን እምባ ማበስ ነው የሚለው ተቋሙ፤ ነገር ግን ብዙ ጊዜ የሚቸገርበት ጉዳይ ማህበረሰቡ ወደ እምባ ጠባቂ ተቋም ማምጣት ያለበትን ጉዳይ አለማወቅ እንደሆነ ነግሮናል፡፡
በዚህ ምክንያት አጠቃላይ አቤቱታዎች 35 በመቶዎቹ አይመለከቱንም ብለን የምንመልሳቸው ናቸው ያሉን የተቋሙ ምክትል እምባ ጠባቂ ዶክተር የኔነህ ስመኝ ናቸው፡፡
Comments