ህዳር 3፣ 2017
በኢትዮጵያ በስኳር ህመም ከሚያዙት ሰዎች መካከል 67 በመቶዎቹ ህመሙ እንዳለባቸው እንደማያውቁ ጥናት አሳየ፡፡
በአለም አቀፉ የስኳር ፌድሬሽን የተደረገው ጥናት እንደሚያሳየው በኢትዮጵያ 2 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የስኳር ህመም አለባቸው፡፡
ከአጠቃላይ ህዝቡ 3.3 በመቶ የሚሆነው ለበሽታው ተጋላጭ ነው፡፡
ይሁንና የስኳር ህመም ቀድሞ ምልክት የማያሳይ በመሆኑ በኢትዮጵያ በየጊዜው በህመሙ ከሚጠቁት ሰዎች 67 በመቶዎቹ ህመሙ እንዳለባቸው እንኳን እንደማያውቁ ጥናቱ አሳይቷል፡፡
በዓለም ዙሪያም 50 በመቶ ተጠቂዎች ህመሙ እንዳለባቸው አያውቁም ተብሏል፡፡
በአፍሪካ ደግሞ ሁለት ሶስተኛ የሚሆኑ ህመሙ ያለባቸው ሰዎች በህመሙ አንደተጠቁ አያውቁም ይላል ጥናቱ፡፡
በተጨማሪም በአለም አቀፍ ደረጃ በዚህ ህመም ከተጠቁ 653 ሚሊዮን ሰዎች 80 በመቶዎቹ ኢትዮጵያ በምትመደብበት በማደግ ላይ ባሉ ሃገራት የሚኖሩ መሆናቸውን ያስቀምጣል፡፡
Comments