በትግራይ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ17,000 በላይ ሰዎች በወባ መያዛቸውን ተነገረ
TRACK

በትግራይ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ17,000 በላይ ሰዎች በወባ መያዛቸውን ተነገረ

Avatar

ታህሣስ 2፣2017

በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች የወባ ወረርሽኝ በስፋት እየታዬ እንደሆነ ይነገራል፡፡

ካለፈው ሁለት ዓመታት በተለየ የወባ ወረርሽኝ ቁጥር መጨመሩን የተለያዩ ቁጥራዊ መረጃዎችም ያሳያሉ፡፡

ለምሳሌም በትግራይ በ2016 ዓ.ም ጥቅምት ወር በሳምንት ከ10,000 በላይ ሰዎች በወባ ወረርሽኝ ሲያዙ እንደነበር የተነገረ ሲሆን በተያዘው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነፃፀር ሥርጭቱ ሰፍቶ በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ17,000 በላይ ሰዎች በወባ መያዛቸውን ሸገር ከክልሉ ጤና ቢሮ ሰምቷል፡፡

ከጥር ወር 2016 ዓ.ም እስከ ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በአጠቃላይ በክልሉ በወባ ወረርሽኝ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ300,000 በላይ መሆኑን ሪፖርት ያሳያል የሚሉት አስተባባሪው ይህም ከዚህ ቀደም ታቶ የማይታወቅ እና ቁጥሩም ከፍተኛ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል፡፡

Comments

Avatar