በይርጋለም ማረሚያ ቤት ለ60 ሰው ተብሎ በተገነቡ ክፍሎች 240 ታራሚዎች ተፋፍገው እንደሚኖሩበት ተነገረ
TRACK

በይርጋለም ማረሚያ ቤት ለ60 ሰው ተብሎ በተገነቡ ክፍሎች 240 ታራሚዎች ተፋፍገው እንደሚኖሩበት ተነገረ

Avatar

ነሐሴ 3፣2016

በይርጋለም ማረሚያ ቤት ለ60 ሰው ተብሎ በተገነቡ ክፍሎች 240 ታራሚዎች ተፋፍገው እንደሚኖሩበት ተነገረ፡፡

በ1945 ዓ.ም ተገንብቶ ላለፉት ለ80 ዓመታት ገደማ ምንም ዓይነት ማሻሻያ ሳይደረግበት በቀጠለው በዚህ ማረሚያ ቤት ታራሚዎች ለተላላፊ በሽታዎች ጭምር እየተጋለጡ መሆኑን ሰምተናል፡፡

በአጠቃላይ 800 ታራሚዎችን ይይዛል ተብሎ የተሰራው ይህ ማረሚያ ቤት በአሁኑ ሰዓት 4,000 ገደማ ታራሚዎችን እንደያዘ ሴንተር ፎር ጀስቲስ የተባለውና በጉዳዩ ላይ የሚሰራው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ተናግሯል፡፡

በጊዜው ለ60 ታራሚዎች ተብለው የተገነቡት ክፍሎችም አሁን 240 ታራሚዎች እያስተናገዱ በመሆኑ ታራሚዎቹ ለተለያዩ ችግሮች እንደተጋለጡ ሰምተናል፡፡

ይርጋለምን ጨምሮ በተለይም በክልሎች ያሉ ማረሚያ ቤቶች፤ ሲገነቡ ታሳቢ ከተደረገላቸው ታራሚ ቁጥር በላይ እያስተናገዱ ነው መባሉንም ሰምተናል፡፡

ማንያዘዋል ጌታሁን ያሰናዳውን በትዕግስት ዘሪሁን

Comments

Avatar