ግንቦት 13 2017
በኢትየጰያ የኤሌክትሪክ መኪኖች በየጎዳናው ላይ ማየት የተለመደ ሆኗል፡፡
መንግስትም በአስር ዓመታት ውስጥ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን 500,000 ለማድረስ ዘርፉ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ይናገራል፡፡
የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እና በዘርፉ ለሚሰማሩ ተቋማት የተለያዩ የፖሊሲ ማበረታቻዎች እየተሰጠ መሆኑን ተከትሎ አምራቾች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እንዲሰሩ መንገድ ከፍቷል ተብሏል፡፡
ከነዚህም መካከል ከቀናት በፊት የቻይናው ጂኤሲ #GAC ግሩፕ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መሸጫ የንግድ ማዕከል ከፍቷል፡፡
በሂደትም ተሸከርካሪዎቹን በኢትዮጵያ የማምረት ውጥን እንዳለው የተነገረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የመኪና ምርቶችን ለኢትዮጵያ ገበያ ማቅረብ መጀመሩን ተናግሯል፡፡
Comments