በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ሴቶች ለሚያጋጥሟቸው ችግሮች መፍትሄ ለመስጠት እየሰራሁ ነው ሲል ሰስተነብል ገሮዊንግ አፍሪካስ ፉድ ሲስተም ተናገረ
TRACK

በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ሴቶች ለሚያጋጥሟቸው ችግሮች መፍትሄ ለመስጠት እየሰራሁ ነው ሲል ሰስተነብል ገሮዊንግ አፍሪካስ ፉድ ሲስተም ተናገረ

Avatar

ጥቅምት 6፣2017

በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ ሴቶች ለሚያጋጥሟቸው ችግሮች መፍትሄ ለመስጠት እየሰራሁ ነው ሲል ሰስተነብል ገሮዊንግ አፍሪካስ ፉድ ሲስተም (Sustainable growing Africa’s food systems/AGRA) የተሰኘ ድርጅት ተናገረ፡፡

ሴቶች በግብርና ዘርፍ ወደ ፊት እንዲወጡ እና ያሉባቸው ችግሮች እንዲቀረፉላቸው ድርጅቱ ቫልዩ ፎር ኸር (VALUE4HER) በተሰኘ ተነሳሽነት ሴቶችን ለማገዝ እየሰራ መሆኑ ተነግሯል፡፡

የሀብት ባለቤት አለመሆናቸው፣ የፖሊሲ ክፍተት መኖሩ፣ የብድር አቅርቦት አለመመቻቸት እና ሌሎችም ችግሮች ሴት ገበሬዎች ከሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች መካከል ነው ተብሏል፡፡

VALUE4HER በሴቶች የሚመሩ የግብርና ንግዶችን ለማበረታታት እና ፍትሃዊ እድገትን ለማምጣት ይሰራል የተባለ ሲሆን በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በዘርፉ የተሰማሩ ሴቶችን ለመደገፍ ስራዎችን መከወን ጀምሯል ተብሏል፡፡

በዚህም በመጀመሪያ ፕሮግራሙ 2,000 በግርናው ዘርፍ የተሰማሩ ሴቶችን መደገፍ ላይ ይሰራል ያሉት ኢትዮጵያ ውሜን ኢን ኮፊ (Ethiopia women in coffee) ዳይሬክተር ሳራ ይርጋ ለነዚህም ሴቶች የአቅም ግንባታ መስጠት፣ ብድር ማመቻቸትን ጨምሮ ሌሎች ድጋፎች ያደርጋል ብለዋል፡፡

Comments

Avatar