TRACK
በኮንሶ ዞን የሠገን ዙሪያ ወረዳ የታጠቁ ሀይሎች ሰሞኑን ባደረሱት ጥቃት 13 ሰዎች ገድለው ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ማውደማቸው ተሰማ
00:00
ነሐሴ 17፣2016
በኮንሶ ዞን የሠገን ዙሪያ ወረዳ የታጠቁ ሀይሎች ሰሞኑን ባደረሱት ጥቃት 13 ሰዎች ገድለው ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ማውደማቸው ተሰማ፡፡
በታጣቂዎቹ ጥቃት ህይወታቸውን ያጡት 8ቱ የፖሊስ አባላት ሲሆኑ 5 ንፁሃንን ሰዎች እንደሆኑ ዞኑ ለሸገር ተናግሯል፡፡
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ በኮንሶ ዞን የሠገን ዙሪያ ወረዳ የታጠቁ ሀይሎች ባሳለፍነው ቅዳሜ ድንገት ጥቃት በመፈፀም የሰገን ከተማን ተቆጣጥረው ለ 5 ቀናት እንደቆዩ የኮንሶ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዩች መምሪያ ሀላፊ ሰራዊት ዲባባ ነግረውናል፡፡
ማንያዘዋል ጌታሁን ያሰናዳውን በፋሲካ ሙሉወርቅ
Comments
00:00