ጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ እና ማገገሚያ ማዕከል የጀመረው ህንፃ ለመጨረስ 1.5 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ተናገረ፡፡
TRACK

ጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ እና ማገገሚያ ማዕከል የጀመረው ህንፃ ለመጨረስ 1.5 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ተናገረ፡፡

Avatar

ታህሳስ 11፣2017

ጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ እና ማገገሚያ ማዕከል የጀመረው ህንፃ ለመጨረስ 1.5 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ተናገረ፡፡

ማዕከሉ እየተገነባ ያለው ባለ ስድስት ወለል ህንፃ ሙሉ ለሙሉ በስሩ እየተረዱ ላሉ ሴቶች ሲሆን ወደፊት ተጨማሪ 2 ባለስድስት ወለል ህንፃ ለወንዶች ማረፊያ እና የእደ ጥበብ ማስተማሪያ ማገገሚያ እና መዝናኛ ማዕከል የያዘ ህንፃ ለመገንባት አቅዷል ተብሏል፡፡

የማዕከሉ መስራች ሊቀህሩያን መለሰ አየለ ግንባታው የተጀመረው ህንፃ ስራ እስካሁን ሲካሄድ የነበረው በራሱ በማዕከሉ አቅም የነበረ ሲሆን ለዚህም 50 ሚሊዮን ብር ወጪ አድርጓል ብለዋል፡፡

ህንፃውን ለማጠናቀቅ የህብረተሰቡ ትብብር ከሌለ ግንባታውን መፈፀም አይቻለንም ፤ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለዚህ ትብብር ሊያደርግ ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

የህንፃው አሰሪ ኮሚቴ አስተባባሪ ኢንጅነር አቤል ተፈራ ‘’አሁን የሚገነባው ባለ ስድስት ወለል ህንፃ በ502 ካሬ ላይ አርፏል’’ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ግንባታው ሲጠናቀቅ ታማሚዎች እና ነርሶችን ጨምሮ እስከ 5,000 ሰው ይይዛል፡፡

Comments

Avatar