መስከረም 23፣2017
ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 3 ወራት ከወርቅ ወጪ ንግድ ያገኘችው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር ከ540 በመቶ በላይ ጭማሪ አለው ተባለ፡፡
ይህን ያለው የብሄራዊ ባንክ ነው፡፡
የብሔራዊ ባንክ ዋና ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ላይ ያደረግነው ለውጥ ያሰብነውን ግብ እየመታ ነው ብለዋል፡፡
ባለፈው ዓመት በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከወርቅ የተገኘው የውጭ ምንዛሪ 58 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነበር ተብሏል፡፡
ዘንድሮ በተመሳሳይ ወቅት ከወርቅ የተገኘው የውጭ ምንዛሪ ግን 488 ሚሊዮን ዶላር ነው ይህም ከ540 በመቶ በላይ ጭማሪ አሳይቷል ሲሉ አቶ ማሞ ምህረቱ አስረድተዋል፡፡
Comments