መስከረም 2፣2017
ከበዓሉ ዋዜማ እስከ ዛሬ መስከረም 2 2017 ዓ.ም ባሉት ቀናት በትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡
የ2017 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል እንዴት አለፈ ስንል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቀናል፡፡
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡን ምላሽ ከዋዜማው ጀምሮ በተከሰቱት የትራፊክ አደጋዎች የ4 ሴቶችና የ2 ወንዶች ሰዎች ይህወት አልፏል ብለዋል፡፡
በዚህም በበዓሉ ዋዜማ ጳጉሜ 5 ቀን በጉለሌ ክፍለ ወረዳ 6 ቀለበት መንገድ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ አንድ የ35 ዓመት ግለሰብ ህይወቱ አልፏል፡፡
Comments