ህዳር 10 2018
ላለፉት 6 ዓመታት በጉምሩክ ተይዘውብኝ የነበሩት ኮምፒውተሮች ተለቀውልኛል ሲል ራዕይ የህፃናት መርጃ ድርጅት ተናገረ፡፡
ይህ የሆነው ጉዳዩን ወደ ሚዲያ ካመጣሁት በኋላ ነውም ብሏል፡፡
ባሳለፍነው ሳምንት የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ህፃናት ለማሰልጠን ሊውል የነበረና በልገሳ ከውጭ ሃገር ያስገባሁት ኮምፒውተር በጉምሩክ ተይዞ 6 ዓመት ሆነው ሲል የህፃናት መርጃ ድርጅቱ ተናግሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከድርጅቱ የኢትዮጵያ ተጠሪ ወ/ሮ ሰሎሜ ኩምሳ እንደሰማነው መረጃው በሚዲያ በተሰራጨ ማግስት ከድርጅቱ የክብር አምባሳደር አትሌት መሰረት ደፋር ጋር በመሆን ድርጅቱ ለጉምሩክ ኮሚሽን ኮምፒውተሮቹ እንዲመለሱለት ያቀረበው ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ አግኝቶ፤ 107 ኮምፒውተሮች፣ እንደ ኪቦርድ፣ ጊታር፣ ድራም ያሉ የሙዚቃ መሳሪያዎችን፣ የልጆች መጫወቻዎችንም ጭምር ተከማችቶ ከነበረበት ተረክበናል ብለዋል፡፡
Comments