ወጣቶች የራሳቸውን ስራ እንዳይፈጥሩ ፈተና የሚሆንባቸው ምንድነው?
TRACK

ወጣቶች የራሳቸውን ስራ እንዳይፈጥሩ ፈተና የሚሆንባቸው ምንድነው?

Avatar

መስከረም 13 2018

ወጣቶች የራሳቸውን ስራ እንዳይፈጥሩ ፈተና የሚሆንባቸው ምንድነው?

መንግስት በየጊዜው ከት/ት ተቋማት ለሚመረቁ ሁሉ ስራ መስጠት ስለማይቻል ወጣቱ የራሱን የስራ እድል ይፍጠር ሲል ይሰማል፡፡

መንግስት ወጣቶችን በሚመለከት ከተቀጣሪነት ወደ ስራ ፈጣሪነት ተሸጋገሩ ቢልም በርካታ ወጣቶች የቢዝነሱ እና የፈጠራ ሃሳቡ ኖሯቸው ሀሳባቸውን መሬት ላይ ለማውረድ የገንዘብና መሰል ችግሮች እጃቸውን አጣጥፈው ተቀጣሪነትን ብቻ እንዲመርጡ እንዳደረጋቸው ይነገራል።

ለመሆኑ አሁን ላይ ወጣቱ የራሱን ስራ እንዲሰራ ወይም መንግስት እንደሚለው ስራ ፈጣሪ እንዲሆን ምን ዓይነት ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥሮለት ይሆን?

ወደ ስራው የገቡት ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎችስ ያሉባቸው ችግሮች ምንድን ናቸው? የኢትዮጵያ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች ማህበር አባላትን አነጋግረናል።

የማህበሩ አባልና ስራ ፈጣሪዋ ፎዚያ መሀመድ ከዓመታት በፊት በዘርፉ የነበሩ ችግሮች እየተቃለሉ የመጡ ቢሆንም አሁንም ግን ችግሮች ሙሉ በሙሉ አልተፈቱም ትላለች።

Comments

Avatar