ከ200,000 ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል የፈጠረ መስክ
TRACK

ከ200,000 ለሚልቁ ሰዎች የስራ ዕድል የፈጠረ መስክ

Avatar

ህዳር 15 2018

ከፍተኛ ሊባል የሚችል ቁጥር ያላቸው ሴቶች በኢትዮጵያ የአበባ እርሻ ልማት የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል።

የዘርፉ ስኬቶች ከሚባሉ ጉዳዮች አንዱም ይኸው የስራ ዕድል ፈጠራ ነው።

እንዲያም ሆኖ የሚሰሙ አንዳንድ ቅሬታዎች አሉ ። ለተመሳሳይ ስራ እኩል ክፍያ ያለማግኘት መብት አለመከበር እና የኬሚካል አጠቃቀም ችግር ይጠቀሳሉ።

በኢትዮጵያ የአበባ እርሻ ልማት ከተጀመረ ሃያ ዓመታት አልፈዋል።

በእነዚህ ጊዜያት ዘርፉ ቀላል የማይባል ዕድገት ማሳየቱን መንግስት እና በስራው የተሰማሩ ባለሃብቶች ይናገራሉ።

ልማቱ ሲጀመር ከ28.5 ሚሊየን ዶላር የማይበልጠው የዘርፉ የአመት ገቢ አሁን ላይ ከ500 ሚሊየን ዶላር በላይ መሆኑ እንደ ማሳያ ይቀርባል።

Comments

Avatar