በኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ለጋሾች ድጋፍ መቀነስ
TRACK

በኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ለጋሾች ድጋፍ መቀነስ

Avatar

ህዳር 24 2018

በኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ለጋሾች ድጋፍ መቀነስ ምክንያት በኤችአይቪ መከላከልና ህክምናው ላይ ተጽዕኖ እንዳይበረታ ካልተሰራ የበሽታውን መከላከል ስራ ወደኋላ እንዳይመልሰው ያሰጋል ተባለ፡፡

ለዚህም በመንግስት እንዲሁም በአገር በቀል ድርጅቶች በኩል የሚሰራው ስራ መጠናከር እንዳለበት ተነግሯል፡፡

የአለም ኤድስ ቀን በኢትዮጵያ እየታሰበ ነው፤ የዘንድሮ ቀን የሚታሰበው ደግሞ ችግሮችን በመቋቋም የኤችአይቪ ኤድስ ( #HIV_AIDS ) ምላሽ ዘላቂነት ማረጋገጥ ላይ አተኩሮ ነው ተብሏል፡፡

የዓለም አቀፍ ድርጅቶች የድጋፍ መቀነስ በተለይም የበሽታው መከላከል ላይ ተጽእኖ ከዚህ በላይ እንዳይሰፋ የሀገር ውስጥ ሀብት በማሰባሰብ አገልግሎቶች እንዳይቋረጡ ማድረግ ላይ መሠራት እንዳለበት የተነግሯል፡፡

በኢትዮጵያ በድጋፍ ላይ የሚሰሩት ዩኤን ኤድስን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት የዓለም ኤድስ ቀንን አስመልክቶ ባሰናዱት አውደ ጥናት ላይ ነው እንዲህ የተባለው፡፡

Comments

Avatar