ሰኔ 18 2017
በዶሮ እርባታ ላይ የተሰማሩ ትናንሽ አርቢሮች ከዘርፉ መውጣታቸው ለእንቁላል መወደድ ምክንያት ሆኗል ተባለ።
አርቢዎቹ ከዘርፉ እንዲወጡ ያስገደዳቸውም የመኖ ዋጋ ውድነት እንደሆነ ሰምተናል።
መኖ አቅራቢ ፋብሪካዎችም ቢሆኑ በጥሬ እቃ እጥረት እና መወደድ ምክንያት እየተቸገሩ መሆኑን ሰምተናል።
በዚህ እና በሌሎች ተደራራቢ ምክንያቶች የእንቁላል መኖ ዋጋ ከፍ ማለቱን ተነግሯል።
አንድ ኩንታል የእንቁላል ጣይ የዶሮ መኖ ከሁለት ወር በፊት ሲሸጥ ከነበረው 4,800 ብር አሁን 5,800 ብር እየተሸጠ መሆኑን ሰምተናል፡፡
በተለይ አቅም የሌላቸው ትናንሽ አርቢዎች እየተቸገሩ በመምጣታቸው ከገበያው ለመውጣት ይገደዳሉ የተባለ ሲሆን በምርት እና ፍላጎት አለመጣጣም ምክንያት አንድ እንቁላል እስከ 25 ብር እንዲሸጥ እድል ፈጥሯል ተብሏል።
Comments