ሚያዝያ 2 2017
ኢትዮጵያ ውስጥ ገብተው መስራት የሚፈልጉ የውጪ ባንኮች 40 ሚሊየን ዶላር ካፒታል ማስመዝገብ አለባቸው ተብሏል።
ገንዘቡ የአገር ውስጥ ባንኮች ሲቋቋሙ ከሚጠየቁት አምስት ቢሊየን ብር ጋር የተቀራረበ ምንዛሪ አለው።
ለመሆኑ የተጠየቀው 40 ሚሊየን ዶላር ካፒታል የውጪ ትላልቅ ባንኮችን ምን ያህል ወደ ኢትዮጵያ ሊጋብዝ ይችላል?
የውጪ ባንኮች ኢትዮጵያ ውስጥ ገብተው እንዲሰሩ የሚፈቅድ አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅደቁ ይታወሳል።
የአዋጁን መውጣት ተከትሎ ደግሞ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ በብሄራዊ ባንክ ይፋ ሆኗል።
መመሪያው የውጭ ባንኮች በኢትዮጵያ ስራ ለመጀመር ከአምስት ቢሊየን ብር ጋር ተቀራራቢ የሆነ ምንዛሪ ያለው 40 ሚሊየን ዶላር ካፒታል ማስመዝገብ እንዳለባቸው ይጠቅሳል።
ስለ ገንዘቡ ምንጭ የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ እንዳለባቸውም መመሪያው ይደነግጋል።
የውጪ ባንኮች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲሰሩ የተፈቀደው በአራት መንገዶች ሲሆን የመጀመሪያው ተቀጥላ ወይም ሰብሲደሪ ባንክ መክፈት ነው።
Comments