በአዲስ አበባ በመንፈቅ ጊዜ ውስጥ በህገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ26,000 ሊትር በላይ ነዳጅ ተወርሷል
TRACK

በአዲስ አበባ በመንፈቅ ጊዜ ውስጥ በህገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ26,000 ሊትር በላይ ነዳጅ ተወርሷል

Avatar

ታህሳስ 24፣2017

በአዲስ አበባ በህገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ26,000 ሊትር በላይ ነዳጅ ተወረሰ፡፡

ነዳጁን ሲሸጡ የተያዙት ማደያዎችና ግለሰቦች ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል፤ የተወረሰው ነዳጅም በህጋዊው ገበያ ተሽጦ ከ2.4 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ መንግስት ካዝና ገብቷል ተብሏል፡፡

ይህ ገቢ የተገኘው በመንፈቅ ጊዜ ውስጥ በአዲስ አበባ ባሉ የነዳጅ ማደያዎች በህግ ከተፈቀደው ውጪ በጄሪካን እየተቀዳ ከተተመነው ዋጋ በላይና ያለ ኤሌክትሮኒክስ መላ ሲሸጥ መሆኑን ተቆጣጣሪው አካል የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ነግሮናል፡፡

Comments

Avatar