ታህሳስ 24፣2017
በአዲስ አበባ በህገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ26,000 ሊትር በላይ ነዳጅ ተወረሰ፡፡
ነዳጁን ሲሸጡ የተያዙት ማደያዎችና ግለሰቦች ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል፤ የተወረሰው ነዳጅም በህጋዊው ገበያ ተሽጦ ከ2.4 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ መንግስት ካዝና ገብቷል ተብሏል፡፡
ይህ ገቢ የተገኘው በመንፈቅ ጊዜ ውስጥ በአዲስ አበባ ባሉ የነዳጅ ማደያዎች በህግ ከተፈቀደው ውጪ በጄሪካን እየተቀዳ ከተተመነው ዋጋ በላይና ያለ ኤሌክትሮኒክስ መላ ሲሸጥ መሆኑን ተቆጣጣሪው አካል የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ነግሮናል፡፡
Comments