ህዳር 25 2018
በግብርናው ዘርፍ ለመሰማራት ፈቃድ ወስደው ሰፈራ መሬት ከወሰዱ ባለሀብቶች እስከ 75 በመቶው ወደ ልማት ሲገቡ አይታይም፡፡
መሬቱ ላይ ለመስራት ሳይሆን በተሰጣቸው የኢንቨስትመንት ፈቃድ የባንክ ብድር ለማግኘት አልመው ወደዚህ ስራ የሚገቡ አሉ ተብሏል፡፡
በኢትዮጵያ 7,000 የሚሆኑ ባለሃብቶች በእርሻ ኢንቨስትመንት ለመሰማራት 2.2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በተለያዩ ክልሎች መውሰዳቸውን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።
ባለሃብቶቹ መሬቱን የወሰዱት ለገበያ የሚውሉ የተለያዩ ሰብሎችን ለማምረት እንደሆነ መረጃው ያመለክታል።
ለግብርና ኢንቨስትመንት ከተሰጠው 2 ነጥብ 2 ሚሊየን ሄክታር መሬት እስከ አሁን ባለሃብቶቹ የለማው ግን 25 በመቶው ብቻ እንደሆነ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ ተናግረዋል።
Comments