ጥቅምት 16፣2017
የአዲስ አበባን የነዋሪነት አገልግሎት ለማግኘት መሸኛቸውን ይዘው የሚጠባበቁ ሰዎች ብዛት 39,000 ደርሷል፡፡
በአዲስ አበባ ሁሉንም የነዋሪነት አገልግሎት ለማግኘት በቅድሚያ የብሔራዊ ዲጂታል(ፋይዳ) መመዝገብ ግዴታ እንደሆነ ከአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲው ሰምተናል፡፡
ከተለያዩ አካባቢዎች መልቀቂያ ይዘው የአዲስ አበባ የነዋሪነት አገልግሎት ለማግኘት ከዚህ ቀደም 6 ወር የሚጠብቁ የነበረ ሲሆን አሁን 3 ወር እንደሚጠብቁም ተነግሯል፡፡
Comments