የካቲት 20፣2016
በኢትዮጵያ በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች እርዳታ ጠባቂ ለሆኑ ሰዎች ለመጪው አንድ ዓመት የሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ 3.24 ቢሊዮን ያስፈልጋል ተባለ።
እርዳታ ጠባቂ ለመሆን የተገደዱት ሰዎች ብዛት 21.4 ሚሊዮን ነው የተባለ ሲሆን የሚፈለገው ገንዘብ ከተገኘ 15.5 ሚሊዮን ሰዎች ድጋፍ ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ሪፖርቱን ይፋ ያደረገው ዩኤን ኦቻ ከሚያስፈልገው 3.24 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 1.54 ቢሊዮን ዶላሩ ለቀለብ መስፈሪያ የሚሆን ነው ብሏል።
ድርቅ፣ ጎርፍ እንዲሁም ጦርነት በኢትዮጵያ ሚሊዮኖችን ለእርዳታ ጠባቂነት ዳርገዋቸዋል።
ንጋቱ ሙሉ
#Ethiopia #ShegerWerewoch #ድርቅ #ጎርፍ #እርዳታ #OCHA
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw
Website: https://www.shegerfm.com/
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comments