በየጊዜው የሚለዋወጡ ህጎች የኢንቨስትመንት መስኩ ተገማች እንዳይሆን ማድረጉን የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ተናገረ።
TRACK

በየጊዜው የሚለዋወጡ ህጎች የኢንቨስትመንት መስኩ ተገማች እንዳይሆን ማድረጉን የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ተናገረ።

Avatar

ህዳር 12 2018

በየጊዜው የሚለዋወጡ ህጎች የኢንቨስትመንት መስኩ ተገማች እንዳይሆን ማድረጉን የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ተናገረ።

የፀጥታ ችግርም እንቅፋት እንደሆነበት ኮሚሽኑ ለህዝብ እንደራሴዎች ተናግሯል፡፡

ኪሚሽኑ ይህን የተናገረው የሶስት ወራት የስራ ክንውን ሪፖርቱን በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ለንግድ እና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ትናንት ህዳር 11 ቀን 2018 ዓ.ም ባቀረበበት ወቅት ነው።

የኢንቨስትመንት ኮሚሽንን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ሪፖርት በንባብ ያቀረቡት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ዳገቶ ኩምቢ ባለፉት 3 ወራት 400 ሚሊዮን ዶላር በተኪ ምርት ወይንም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት ታቅዶ መፈጸም የተቻለው ግን 211 ሚሊዮን ዶላር ወይንም የእቅዱን 53 በመቶ እንደሆነ አስረድተዋል።

Comments

Avatar