ሚያዝያ 30 2017
የዲኤችኤል #DHL ኢትዮጵያ ሰራተኞች ዛሬ የስራ ማቆም አድማ ማድረጋቸው ተሰማ፡፡
የሰራተኛ ማህበር በማቋቋማችን ከአስተዳደሩ ጋር አለመግባባት ተፈጥሮ ቆይቷል ያሉት ሰራተኞቹ አሁን ያለውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም የሚያስችል የደሞዝ ጭማሪም ተከልክለናል ይላሉ፡፡
ጉዳዩን በመሀል ሲያሸማግል የቆየው የትራንስፖርትና መገናኛ ሰራተኛ ማህበር ፌዴሬሽን ጉዳዩን ለአለም አቀፍ የትራንስፖርት ፌዴሬሽን አሳውቂያለሁ ብሏል፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
Comments