በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ከተለያዩ አካባቢዎች የተፈናቀሉ፤ 2,500 ሰዎች በዲጋ ወረዳ ተጠልለው ይገኛሉ ተብሏል፡፡
TRACK

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ከተለያዩ አካባቢዎች የተፈናቀሉ፤ 2,500 ሰዎች በዲጋ ወረዳ ተጠልለው ይገኛሉ ተብሏል፡፡

Avatar

ግንቦት 12፣2016

በምስራቅ ወለጋ ተፈናቅለው ለሚገኙ ሰዎች እርዳታ እንዲደረግ ተጠየቀ፡፡

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ከተለያዩ አካባቢዎች የተፈናቀሉ፤ 2,500 ሰዎች በዲጋ ወረዳ ተጠልለው ይገኛሉ ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ሲቭል ማህብረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን፤ ጄፕሮ ከተሰኘ ድርጅት ጋር በመተባበር ለእነዚህ ተፈናቃዮች ድጋፍ አድርጓል፡፡

በአካባቢው በነበረው የጸጥታ ስጋት ምክንያት ረጂ ድርጅቶች ወደ ቦታው ገብተው እርዳታ ለማድረስ ፈርተው ቆይተዋል ተብሏል፡፡

በአሁን ሰዓት በአንፃራዊነትም ቢሆን በአካባቢው እርዳታ ለማድረስ አስቻይ ሁኔታ እንዳለ ተነግሯል፡፡

ስለዚህም በብዙ ችግር ውስጥ ለሚገኙ ተፈናቃዮች፤ ረጂ አካላት እጃቸውን እንዲዘረጉ ተጠይቀዋል፡፡

የሲቨል ማህበረሰብ ድርጀቶች ባለስልጣን በበኩሉ ለተረጂዎች የሚውል 3 ሚሊዮን ብር መድቤለሁ ብሏል፡፡

ከዚህም ብር ውስጥ 1 ሚሊዮኑ ለዲጋ ወረዳ ተፈናቃዮች እርዳታ ውሏል መባሉን ሰምተናል፡፡

በባለስልጣኑ የፈንድ አስተዳደርና ንብረት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሀ/ማርያም አየለ፤ በአካባቢው እርዳታ የሚሹ ሰዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅትም ሆኑ ሌሎች ማናቸውም ረጂ አካላት ለተፈናቃዮቹ ትኩተት እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል፡፡

እርዳታውን በማስተባበር ያደረሰው የጄፕሮ(Jiret Peace And Reconciliation Organization) ዳይሬክተር ዳዊት ደመቀ፤ በምስራው ወለጋ የሚገኙ ተፈናቃዮችን ስፍራው ድረስ ሄደን ተመለከተናል ብለዋል፡፡

ማንያዘዋል ጌታሁን ያሰናዳውን በያሬድ እንዳሻው

Comments

Avatar