TRACK
ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ ሀያላን ሀገራት የሚጣልባቸው ካሣ እንዲከፍሉ በህግ ለማስገደድ የሚያስችል ስራ ለመስራት እንቅስቃሴ መጀመሩን ተነገረ፡፡
ጥቅምት 20፣2017
ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ ሀያላን ሀገራት የሚጣልባቸው ካሣ እንዲከፍሉ በህግ ለማስገደድ የሚያስችል ስራ ለመስራት እንቅስቃሴ መጀመሩን ተነገረ፡፡
ይህ የተባለው የክርስቲያን በጎ አድራጎት እና ልማት ማኅበራት ህብረት እያደረገው ባለው የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ላይ ነው፡፡
የህብረቱ ዋና ዳይሬክተር ንጉሱ ለገሰ(ዶ/ር) የጀርመን መንግስት በማደግ ላይ ካሉ ሀገራት ጋር በመሆን ሀያላን ሀገራት በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚጣልባቸው ካሳ በህግ እንዲከፍሉ ለማድረግ አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለዋል፡፡
በዚህ እንቅስቃሴ ላይ ኢትዮጵያ ጨምሮ ብራዚል ህንድ እና ሌሎች በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት አብረው እየሰሩ መሆኑን ሰምተናል፡፡
ዶክተር ንጉሱ ይህንን ለማስፈፀም ሀገራቱ አሁን እየመከሩ ነው ያሉ ሲሆን በተለይም በዓለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት ካሣ አንከፍልም የሚሉ ሀገራትን ለመጠየቅ አቅደን እየተንቀሳቀስን ነው ሲሉ ያስረዳሉ፡፡
በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ሀገራት በከፍተኛ ደረጃ ጉዳት እየገጠማቸው ነው የሚሉት ዶክተር ንጉሱ በዚህም ምክንያት ገበሬው ችግር ውስጥ እየገባ ነው ለዚህም የክርስቲያን በጎ አድራጎት እና ልማት ማህበራት ህብረት ትኩረት ሰጥቶ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለዋል፡፡
Comments