በአረብ ሀገራት ያሉ ኢትዮጵያዊያን አድራሻቸው በአግባቡ ተመዝግቦ እና መብታቸው ተከብሮ እንዲሰሩ ያግዛል የተባለለት ስምምነት ተፈረመ
TRACK

በአረብ ሀገራት ያሉ ኢትዮጵያዊያን አድራሻቸው በአግባቡ ተመዝግቦ እና መብታቸው ተከብሮ እንዲሰሩ ያግዛል የተባለለት ስምምነት ተፈረመ

Avatar

መስከረም 24፣2017

በተለይ በአረብ ሀገራት ያሉ ኢትዮጵያዊያን አድራሻቸው በአግባቡ ተመዝግቦ እና መብታቸው ተከብሮ እንዲሰሩ ያግዛል የተባለለት ስምምነት ተፈረመ።

ስምምነት የተደረገውም በኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን እና በኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ኤጀንሲ አሰሪዎች ፌዴሬሽን በኩል ነው።

ስምምነቱም ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት ለመሄድ ህገ-ወጥ የውጭ ሀገራት ጉዞን ለማስቀረትና በህጋዊ መንገድ የሚሄዱ ዜጎችን መረጃ ለማወቅ የሚያግዝ፣ መብት እና ደህንነታቸውንም የሚያስጠበቅ ነው ተብሏል።

ከዚህ ቀደም በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በአሰሪዎቻቸው የሚደርስባቸው እንግልት እና እስራት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑም ተነግሯል።

Comments

Avatar