መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም የሰላም እጦት ያሉባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎችን ጨምሮ ትምህርት ተጀምሯል
TRACK

መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም የሰላም እጦት ያሉባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎችን ጨምሮ ትምህርት ተጀምሯል

Avatar

መስከረም 30፣2017

መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም የሰላም እጦት ያሉባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎችን ጨምሮ ትምህርት ተጀምሯል፡፡

የሰላም እጦት ከነበሩባቸው እና አሁንም ድረስ ችግሩ ከቀጠሉባቸው አካባቢዎች መካከል አማራ ክልል አንዱ ነው፡፡

የመማር ማስተማሩ አሁን እየታየ ያለው የሰላም እጦት ስራዬን እንዳያስተጓጉለው ያሰጋኛልም ብሏል፡፡

በክልሉ ያሉ ትምህርት በቤቶችን በሙሉ ወደ ስራ ለማስገባት እንጥራለን የሚለው የክልሉ ትምህርት ቢሮ የሰላም እጦቱ አሁን ስጋት በፈጠረብን ልክ የሚዘልቅ ከሆነ ግን የመማር ማስተማር ሂደቱ ችግር ያጋጥመዋል ብለዋል፡፡

የዚህ ሁሉ ችግር የሚንፀባረቀው ተማሪዎች ላይ ነው የሚሉት የክልሉ ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን የትምህርት አቀባበላቸው እንዲቀንስ ሴቶች ደግሞ ያለ እድሜ ጋብቻ እንዲጋለጡ ያደርጋል ይላሉ፡፡

በተጨማሪም ባሳለፍነው የትምህርት ዘመን በሰላም እጦት ምክንያት የ6ተኛ፣ የ8ተኛ እና የ12 ክፍል ፈተና ያልተፈተኑ ተማሪዎች ነበሩን ያሉት ሀላፊው በዘንድሮው አመት በሁለተኛ ዙር እንዲፈተኑ እናደርጋለን ብለዋል፡፡

Comments

Avatar