ጥቅምት 6፣2017
በቡና ምርት ላይ የተሰማሩ አርሶ አደር ሴቶችን የሚደግፍ ተቋም ባሉበት አካባቢ ባለመኖሩ ምርቱም ላይ ሆነ አምራቾቹን እየጎዳ ነው ተባለ፡፡
ይህ ደግሞ በቡና ምርት ላይ የተሰማሩ ሴቶች ከእርሻ ጀምሮ ቡናው ለገበያ እስኪቀርብ ድርስ የሚኖራቸው ተሳትፎ በእጅጉ ይቀንሳል ተብሏል፡፡
ምርቱን ከማምረት የሚጀምረውን ስራ ሴቶች ቢከውኑም ምርቱ ወደ ገበያ በሚወጣበት ወቅት ግን እንብዛም አይታዩም፡፡
ይህንን ያለው ኢትዮጵያን ውሜን ኢን ኮፊ (Ethiopia women in coffee) አስጠናሁት ባለው ጥናት ነው፡፡
በጥናቱም ሴቶች በቡና ማምረት ዘርፉ ላይ ያላቸው ተሳትፎ እስከ 90 በመቶ ነው ነገር ግን ምርቱ ወደ ገበያው ሲወጣ ተሳትፎአቸው ወደ 70 በመቶ ይወርዳል ተብሏል፡፡
Comments