ታህሳስ 24፣2017
የዋጋ ግሽበትን በተመለከተ መንግስት የሚያወጣውን አሃዛዊ መረጃ ገበያ ላይ ካለው የሸቀጦች ዋጋ ጋር እያነፃፀሩ እንዴት ነው ነገሩ? የሚሉ ብዙዎች ናቸው፡፡
ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ግሽበቱ በ5 ዓመት ከታየው ሁሉ ዝቅተኛ ሆኖ 16 በመቶ ወርዷል ይላል፡፡
የምጣኔ ሐብት ባለሞያዎች በበኩላቸው የሰዎች የመግዛት አቅም መዳከሙን መሰረታዊ የተባሉ ሸቀጦች ዋጋ አሁንም ከፍተኛ መሆኑን በማንሳት መንግስት ትክክለኛ የዋጋ ግሽበት ቅናሽ እንዲመጣ ይሰራ ዘንድ ይመክራሉ፡፡
Comments