ሐምሌ 9፣ 2016
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከተቋቋሙበት አንዱ አላማ፤ የማህበረሰብ አገልግሎት መስጠት ቢሆንም እምብዛም እየሰሩበት አይደለም፡፡
በተለይም ዩኒቨርሲቲዎቹ በተቋቋሙበት አከባቢ ከለው ማህበረሰብ ጋር ተቀራርበው እንዲሰሩና ለችግሮች መፍትሄ እንዲሰጡ ጥናትና ምርምር ያደርጋሉ ተብሎ ቢጠበቅም ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ ሲሆን አይስተዋል ተብሏል፡፡
በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የዩኒቨርሲቲዎችና የማህበረሰብ ጉድኝትን በተመለከተ ኃሳባቸውን ያጋሩ ምሁራን እንደሚሉት ኢትዮጵያ ውስጥ የዩነቭስቲዎችና የማህበረሰቡ ጉድኝት በጣም ደካማ ነው ብለዋል፡፡
ለዚህም እንደ ምክንያት የተነሱ ሀሳቦች ተቀራርቦ አለመስራት ዩንቨርስቲዎች አካባቢ እኛ ብቻ እናውቃለን የሚል እሳቤ በመምህራን ዘንድ መኖሩ እና ባለሀብቱ ደግሞ ለምርምር ተቋሙ ራሱን ዝግ በማድረግ ድጋፍ መንፈጋቸው የሚሉት ተነስተዋል፡፡
Comments