ፕራይም ካፒታል አክሲዮን ማህበር የኢንቨስትመንት ባንክ  ፈቃድ አገኘ።
TRACK

ፕራይም ካፒታል አክሲዮን ማህበር የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ።

Avatar

ሚያዝያ 13/ 2018

ፕራይም ካፒታል አክሲዮን ማህበር የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ።

በዚህም ፕራይም ካፒታል አክሲዮን ማህበር የኢንቨስትመንት ፍቃድ ያገኘ ስድስተኛው ባንክ ሆኗል፡፡

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለፕራይም ካፒታል አ.ማ. የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪነት ፈቃድ የሰጠ ሲሆን በዚህም ድርጅቱ ከባንክ ቡድን ውጭ በሆነ የኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ እንዲሠራ ፈቃድ ሰጥቶቷል።

በተጨማሪም ባለስልጣ መ/ቤቱ ለፕራይም ካፒታል አ.ማ. አራት ተሿሚ እንደራሴዎችም ፈቃድ የሰጠ ሲሆን የዘጠኝ የቦርድ አባላት ሹመትንም አጽድቋል።

የአገልግሎት ሰጪነት ፍቃዱም በዛሬው በይፋ የተሰጠ ሲሆን ይህም በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን የተፈቀደላቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ጠቅላላ ቁጥር ወደ አስራ ሰባት ፣ እንዲሁም የኢንቨስትመንት ባንኮችን ቁጥር ወደ ስድስት ከፍ አድርጎታል።

Comments

Avatar