TRACK
ከኢትዮጵያ ህዝብ 68.7 በመቶው በድህነት ውስጥ እንዳለ የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት ሪፖርት አሳይቷል
ህዳር 18፣2017
ከኢትዮጵያ ህዝብ 68.7 በመቶው በድህነት ውስጥ እንዳለ የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት(UNDP) ያወጣው ሪፖርት አሳይቷል፡፡
በዚህ UNDP ባወጣው የሀገራት የድህነት ምጣኔ ሪፖርት በገጠሩ የኢትዮጵያ ክፍል ድህነቱ የከፋ እንደሆነና 79 በመቶ እንደሚደርስ አስቀምጧል፡፡
ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ከUNDP ጋር በመሆን ባደረጉት በዚህ ጥናት ከዚህ በፊት በተመድ የተቀመጠውን አንድ ሰው ደሃ ለመባል ከ2.15 ዶላር ወይም በቀን ከ250 ብር በታች የሚያገኝ መሆን አለበት የሚለውን በመቀልበስ፤ በዋናነት 3 ትልልቅ መለኪያዎችን (የትምህትርት፣ የጤናና የአኗኗር ሁኔታ) በማስቀመጥ በእነዚህ ስር ደግሞ 10 መለኪያዎችን በማከል የ112 ሀገራትን የድህነት ምጣኔ አስቀምጧል፡፡
ኢትዮጵያ አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ እንዳለባትም አሳስቧል።
ሪፖረርቱን መሰረት አድርገን ቀጣዩ የኢትዮጵያ የቤት ስራ ምን ሊሆን ይገባል? በሚለው ጉዳይ ዙሪያ በዘርፉ ለረጅም ዓመታት የሰሩትና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምግብና ኒውትሪሽን ማዕከል ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት አሻግሬ ዘውዱን ጠይቀናል፡፡
Comments