ሰኔ 24 2017
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የደንበኞቼ ቁጥር 10 ሚሊዮን ደርሷል፣ ይህም ከፍተኛ ስኬት ነው አለ፡፡
ኩባንያው የኢትዮ ቴሌኮም ማማዎች ላይ ለሚያስቀምጠው ኔትወርክ ማሰራጫ በየወሩ 3 ሚሊዮን ዶላር እየከፈለ መሆኑንም ሰምተናል፡፡
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ግማሹን የሀገሪቱን ህዘብ ማስጠቀም የሚያስችል ኔትወርክ መዘርጋቱን ዛሬ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል፡፡
አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ፍቃድ ከወሰደ አራት ዓመት አንደሞላው ያስታወሰው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፤ ቢዚህ ጊዜም ከ300 ቢሊዮን ብር በላይ ኢንቨስት አንዳደርገ ዋና ስራ አስፈጻሚው ዊም ቫንሄለቱት አስረድተዋል፡፡
Comments