ሰኔ 24 2017
ከዚህ ቀደም የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች ቢኖሩም በወቅቱ ባለመጠናቀቃቸው ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ተባለ፡፡
መንግስት ለመንገድ ፕሮጀክቶች የሚደለድለው በጀት ይበል የሚያሰኝ ቢሆንም አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች የበለጠ ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ተነስቷል፡፡
ይህ ጥያቄ የተነሳው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2018 ረቂቅ በጀት ላይ በሚያደርገው ውይይት ላይ ነው፡፡
ሁለት ክልሎችን ያገናኛል የተባለው የነቀምት ቡሬ መንገድ ግንባታ እስካሁን ያልተጠናቀቀ መሆኑን ያነሱት የምክር ቤት አባሉ አቶ ብዙአየሁ ደገፋ ሌላኛው ጋምቤላን እና ደንቢዶሎን የሚያገናኘው የመንገድ ግንባታም ስራው አለመጀመሩን አንስተዋል፡፡
በሌላ በኩል እቅድ የተያዘላቸው የመንገድ ፕሮጀክቶች በ2018 በጀት ዓመት ውስጥ ያልተካተቱ መኖራቸውን ያነሱት የምክር ቤት አባሉ ለእነሱ ወደፊት ምን እንደታሰበ ጠይቀዋል፡፡
Comments