TRACK
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ከ10,000 በላይ የቀድሞ የጉህዴን እና የቤህነን ታጣቂዎች ሰልጥነው ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረጉን ተናገረ።
ነሀሴ 21 2017
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ከ10,000 በላይ የቀድሞ የጉህዴን እና የቤህነን ታጣቂዎች ሰልጥነው ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረጉን ተናገረ።
የስራ ዕድሉ የተፈጠረላቸው ሰዎች ውጤታማነት ግን ይለያያል ብሏል።
የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጉህዴን) እና የቤኒሻንጉል ሕዝቦች ነጻነት ንቅናቄ(ቤህነን) ከሶስት ዓመት በፊት ከክልሉ መንግስት ጋር የሠላም ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።
የስምምነቱ አንዱ ይዘት የሁለቱ ቡድኖች የቀድሞ ታጣቂዎች ስልጠና ወስደው በተለያዩ ስራዎች እንዲሰማሩ የክልሉ መንግስት ያደርጋል የሚል ነው።
በዚሁ መሰረት እስከ አሁን ከ10,000 በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች ሰልጥነው በተለያዩ ስራዎች እንደተሰማሩ የክልሉ የስራ እና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱሰላም ሸንገል ተናግረዋል።
Comments