ነሀሴ 21 2017
በቅርቡ የፀደቀውና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ያበረታታል የተባለው የስታርት አፕ አዋጅ በጤናው ዘርፍ ለሚከወኑ የተሻሻሉና ዘመናዊ አሰራሮችን ለመተግበር ያግዛል ተባለ፡፡
በጤና ዘርፉ ከሚሰጡ አገልግሎቶችም ስምንቱ በተለይ በኢኖቬሽን የተደገፈ አሰራር እንዲከተሉ እየተደረገ ነው ተብሏል፡፡
በተለያዩ የጤና አገልግሎት መስጫዎች ላይ ዘመናዊ አሰራሮችን ለመከተል እና በተለይም አገልግሎቶችን ከማሻሻል አኳያ የጤና ኢኖቬሽን ላይ ትኩረት ማድረጉን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡
Comments