መስከረም 6 2018
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከብዙ ሀገራት ምሳሌ ያደረጋትንና የዜጎቿን ጤና ለመጠበቅ ህዝብ በተሰበሰበባቸው ቦታዎች ትንባሆ ማጨስን የሚከለክል ህግ ስራ ላይ ብታውልም አፈጻጸሙ ግን የሚጠበቀውን ያህል አይደለም ተባለ፡፡
ትምባሆ እና የትምባሆ ምርቶችን ማጨስን በተለይ በህዝብ መዝናኛ ቦታዎች እንዲሁም በነጠላ መሸጥን ህጉ ቢከለክልም ተከታትሎ ማስፈፀሙ ላይ ግን ክፍተቶች እንደሚታዩ ተነግሯል፡፡
ትምባሆ በጤና ላይ የሚያስከትላቸውን ጉዳቶች ለማስቀረት የወጣውና ኢትዮጵያ በብዙ መልኩ የምትመሰገንበት ህግ በስራ ላይ ቢሆንም በነጠላ መሸጥ እና ሌሎች ተመሳሳይ ህጉን የሚጥሱ ድርጊቶች ግን አሁንም እንደሚታየዩ የሚናገሩት በጉዳዩ ላይ የሚሰራው የማቴዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ መስራችና የበላይ የሆኑት አቶ ወልዱ በቀለ ናቸው፡፡
Comments