00:00
ነሀሴ 3 2017
ከተሽከርካሪዎች በሚወጣ በካይ ጋዝ የሚደርስ የአየር ብክለትን ለመከላከል በኢትዮጵያ የሚዘወሩ ተሽከርካሪዎች ብክለት መጠን የሚቆጣጠር አስገዳጅ መመሪያ በሁለት ወራት ውስጥ ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑ ተነገረ፡፡
በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በዚህ ዓመት መጋቢት ወር ላይ የተሰናዳው መመሪያ በተሽከርካሪዎች የበካይ ጋዝ ልቀት ምክንያት የሚደርስ የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል ተሽከርካሪዎች ይህንን የሚቆጣጠር ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ የሚያስገድድ ነው ተብሏል፡፡
መመሪያው ወደ ስራ ሲገባ ተሽከርካሪዎች አመታዊ የቴክኒክ ብቃት ምርመራ ማረጋገጫ ለማግኘት በተሽከርካሪው ላይ በካይ የጋዝ ልቀትን የሚቀንስ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ መግጠም ወይም የተሽከርካሪው የበካይ ጋዝ ልቀት መጠን ከተቀመጠው መስፈርት ያለፈ መሆን እንደሌለበት ተነግሯል፡፡
Comments
00:00