ሐምሌ 21 2017
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 60 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች ጤንነቱ ባልተጠበቀ መልኩ ጽንስ እንደሚያቋርጡ ተነገረ፡፡
ወጣት ሴቶች ከገጠሪቱ የሀገሪቱ ክፍል ወደ ክልሉ ከተሞች ለስራ ብለው የሚመጡ እንዳሉ እና በዚህም ላልተፈለገ እርግዝና እንደሚጋለጡ ከክልሉ ጤና ቢሮ ሰምተናል፡፡
በዚህም በወር ከ1,000 በላይ የሆኑ ሴቶች ጽንስ እንደሚያቋርጡ ተነግሯል፡፡
ጽንስን በጤናማ መንገድና በተፈቀደው መሰረት በጤና ተቋማት የሚያቋርጡ ቢኖሩም ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት በቤታቸው እና ጤንነቱ ባልተጠበቀ መልኩ የሚያቋርጡ እንዳሉ ሰምተናል።
በአጠቃላይ በክልሉ በህግ በተፈቀደ እና ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ ጽንሰን የሚያቋርጡ አርባ በመቶ ብቻ እንደሆኑ የነገሩን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ውስጥ የቤተሰብ ዕቅድ እና የአፍላ ወጣቶች ፕሮግራም አስተባባሪ የሆኑት አቶ ወንድሙ ናቸው፡፡
በክልሉ ከ32 በላይ ብሄረሰቦች የሚኖሩበትን እንደመሆኑ ጤንነቱ በተጠበቀ መልኩ ጽንስን ማቋረጥ የሚያውቁ እንዳሉ ሁሉ መረጃው ደግሞ ፍጹም የሌላቸው እንዳሉም አቶ ወንድሙ ነግረውናል፡፡
Comments
awesome. have a great week. Amen/Allah. Greetings from south africa