ሐምሌ 21 2017
በኢትዮጵያ ካሉ ወደ 5,000 ገደማ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ውስጥ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን ተልዕኮና ዓላማ ተረድተው አብረውት እየሰሩ ያሉት ጥቂቶች ብቻ ናቸው ተባለ፡፡
ይህን ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ነው፡፡
ምክር ቤቱም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የኮሚሽኑን ዓላማ ካለመረዳትና በፋይናንስ እጥረት ምክንያት በሚፈለገው ልክ በአገራዊ ምክክሩ ላይ እየተሳተፉ እንዳልሆነ አስረድተዋል፡፡
በምክሩ ላይ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሚፈለገው ደረጃ በንቃት አለመሳተፍ እንደሚያሳስበው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ተናግሯል፡፡
Comments